Asset Publisher

null የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

መጋቢት 05/2016 . (የገቢዎች ሚኒስቴር)

የገቢዎች ሚኒስቴር አመራሮች የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ለማዘመን በሚያስችል ረቂቅ ሰነድ ዙሪያ ከታክስ ትራንስፎርሜሽን /ቤት አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

በምክክር መድረኩ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለግብር ከፋዮች ፈጣንና ተደራሽ አገልግሎት ከመስጠት አኳያ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ ነው ያሉት የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ / መሰረት መስቀሌ ሆኖም አጠቃላይ የታክስ ስርዓቱን ከማዘመን አኳያ ብዙ መስራት እንደሚጠይቅ ገልፀዋል፡፡

ዘመናዊ የታክስ አስተዳደር ስርዓት ለመዘርጋት በተከናወኑ በርካታ ስራዎች ከዓመት ዓመት የሚሰበሰበው ታክስ እያደገ ቢመጣም ከአህጉራዊና ዓለማቀፋዊ መለኪያዎች ጋር ሲነጻጸር ብዙ መስራት እንደሚጠይቅ በውይይቱ ተነስቷል፡፡

ለዚህ ደግሞ አጠቃላይ የታክስ ስርዓቱን ማዘመንና በታክስ አስተዳደሩ ዙሪያ የሚታዩ ማነቆዎችን ለመፍታት አሰራሮችን በቴክኖሎጂ ማስደገፍ የፖሊሲ ማሻሻያ የሚያስፈልጓቸው የታክስ ህጎችን መፈተሽ እንደሚገባም ሚኒስትር ዴኤታዋ አክለው አንስተዋል፡፡

በውይይቱ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ያሉ ችግሮችን በመለየት ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ በማድረግ የሀገር ውስጥ ገቢን ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የኢ-ታክስ እና -ፋይሊንግ አሰራርና አጠቃቀምን በማሻሻል ረቂቅ ሰነዱ ተጠናቆ ወደ ተግባር ሲገባ የታክስ አስተዳደሩን በማዘመን የገቢ አሰባሰቡን እንዲያድግ ያስችላል ተብሏል፡፡