የገቢዎች ሚኒስቴር ጽ/ቤት እና ተጠሪ የመ/ቤቱ ዳሪክቶሬቶች የስድሰት ወር የሰራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ
16/2016 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር)
በግምገማው ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ ወ/ሮ ሂሩት መብራቴ ዘርፉ በስድስት ወራት ያከናወናቸው ተግባራት ለቀጣይ ስራዎች ስንቅ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ በሚኒሰቴር ጽ/ቤት እና ተጠሪ የሆኑ ዳሪክተሬቶች የሰራ አፈፃፀም አበረታች ውጤት እንደነበረም ገልፀዋል፡፡
ለጽ/ቤቱ ተጠሪ የሆኑት ዳሪክተሬቶች እና አማካሪዎች ፣ ቡድን መሪዎች እና የስራ ሂደት አስተባባሪዎች በተገኙበት በተካሄደው ይኸው የግምገማ መድረክ በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል፡፡
ከነዚህም መካከል የፌዴራል ዋና ኦዲተርና እና የውሰጥ ኦዲት ግኝቶችን በመከታተል እርምት ማድረግ፣ ሙስናንና ብልሹ አሰራሮችን ማረምና መከታተል፣ የኮምንኬሽን ሰራዎችን የበለጠ ዘመናዊነትን ተላብሶ እንዲሄድ ማድረግ፣ ፕሮጀክት አሰተዳደር እና አፈፃፀም ጠንካራ ውጤታማ እና ወቅታዊ ሆኖ ተፈፃሚ በሚሆንበት ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መሰራት እንደሚገባ ተነስቷል፡፡
ከሀገር ውሰጥ እና ከውጪ አጋሮች ጋር ተቀናጅቶ መስራት እና የጥናት ሰራዎች ወደ መሬት ወርደው ተፈፃሚ በሚሆኑበት ጉዳዮች ዙሪያ በዝርዝር ውይይት ተደርጎ አቅጣጫ ተሰጥቶበታል፡፡
በመጨረሻም የገቢዎች ሚኒስቴር የጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሂሩት መብራቴ በጽ/ቤቱ ተጠሪ የሆኑ ዳይሬክቶሬቶች ዕቅድ አፈፃፀም ላይ አሰተዋፅ ላበረከቱ እና ለግምገማው ተሳታፊዎች በሙሉ ምሰጋናቸውን አቅርበዋል ፡፡