ደረሰኝ ሳይዙ ሸቀጦችን ጭነው በሚንቀሳቀሱት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

Nested Applications

Asset Publisher

null ደረሰኝ ሳይዙ ሸቀጦችን ጭነው በሚንቀሳቀሱት ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው

የታክስ ሕጉ ማንኛውም ነጋዴ ወይም አገልግሎት ሰጪ ግብይት ካከናወነ በኋላ ደረሰኝ እንዲቆርጥ ቢያስገድድም ደረሰኝ የማይሰጡ እያጋጠሙ በመሆኑ የገቢዎች ሚኒስቴር እርምጃ ሊወስድ እንደሆነ በሚኒስቴር /ቤቱ የታክስ ማጭበርበርና ምርመራ ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ገዙ አስታወቁ፡፡

አንድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ሽያጭ በሚከናወንበት ጊዜ የተጨማሪ እሴት ታክስን 15 በመቶ ጨምሮ ከገዢው ወይም ከተጠቃሚው ለመንግስት ታክስ እንዲሰበስብ በሕጉ ውክልና መሰጠቱን ኃላፊው አስረድተዋል፡፡ ይሁንና በሀገራችን አገልግሎት ሰጪም ሆኑ በየደረጃው ያሉ የንግዱ ማህበረሰብ የታክስ ሕጉን ተከትለው እንደሚሠሩ ሁሉ ደረሰኝ የማይሰጡ መኖራቸውን አቶ ሲሳይ ጠቁመዋል፡፡

ከነዚህ መካከል ሸቀጦች እና ንብረቶች የሚያጓጉዙ እና ጫኝ ድርጅቶች መሆናቸውን ጠቅሰው ሸቀጥ ከመጫናቸው በፊት ሕጋዊ ሰነድ መኖርና አለመኖሩን እያረጋገጡ መሄድ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡ ይህንኑ ተቋሙ ወደ እርምጃ ከመግባቱ በፊት በማስታወቂያ እና በሌሎች የማስተማሪያ መንገዶች የማስገንዘብ ሥራ እንደሚሠራ አመልክተዋል፡፡ ሁሉም ክልሎች በዚህ ላይ በትኩረት እንዲሠሩ አቅጣጫ ለመስጠት መታሰቡን ጠቅሰው በየትኛውም ደረጃ ያሉ የሕግ አስከባሪ አካላት ጭነቶች በሚጓጓዙበት ጊዜ ህጋዊ ሰነድ መያዛቸውን እንዲያረጋግጡ እንደሚደረግም አብራርተዋል፡፡

በታክስ ሕጉ መሰረት አንድ ጭነት ሕጋዊ ሰነድ ሳይኖረው ሲንቀሳቀስ ከተያዘ በዋናነት የጭነቱ ባለቤት ሸቀጡን ከየት እንዳመጣ ማስረጃ መስጠት ያለበት ሲሆን ይህ ሳይሆን ሲቀር ወደ ኋላ በመሄድ ሸቀጡን ያለደረሰኝ የሸጠው አካል ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እና የሕግ ተጠያቂነት እንደሚያስከትልበት አስታውቀዋል፡፡

Asset Publisher

Asset Publisher

ዜና

  • የገቢዎች ሚኒስቴር የሁሉም ክልሎች የገቢ ዘርፍ አመራሮች በታክስ ምንነት፣ ህጎችና አዋጆች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና Wed, 4 Jan 2023
የገቢዎች ሚኒስቴር የሁሉም ክልሎች የገቢ ዘርፍ አመራሮች በታክስ ምንነት፣ ህጎችና አዋጆች ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና
  • ግብር መክፈል የኩራት ምንጭ መሆኑን የሚያምን ማህበረሰብ እንዲፈጠር እንሰራለን! ----------ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ (በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ) Wed, 4 Jan 2023
ግብር መክፈል የኩራት ምንጭ መሆኑን የሚያምን ማህበረሰብ እንዲፈጠር እንሰራለን! ----------ወ/ሮ መሰረት መስቀሌ (በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ)
  • የሀገራችንን ወጪ በታክስ ገቢ ለመሸፈን የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና ከፍተኛ ነው -- ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ (የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ) Wed, 4 Jan 2023
የሀገራችንን ወጪ በታክስ ገቢ ለመሸፈን የታማኝ ግብር ከፋዮች ሚና ከፍተኛ ነው -- ወ/ሮ መሠረት መስቀሌ (የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ)

የኤሌክትሮኒክስ ታክስ የማስታወቂያ ዘዴ /E-tax/ ማሻሻያ የተደረገባቸው የታክስ ማስታወቂያ ቅፆች

Asset Publisher

Nested Applications

Asset Publisher

.