የጉምሩክ ኮሚሽን ያከናወናቸው የለውጥ ተግባራት ለሌሎች ሴክተር መ/ቤቶች ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)

Nested Applications

Asset Publisher

null የጉምሩክ ኮሚሽን ያከናወናቸው የለውጥ ተግባራት ለሌሎች ሴክተር መ/ቤቶች ምሳሌ የሚሆኑ ናቸው ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)

የገቢዎች ሚኒስትር ክብርት / ዓይናለም ንጉሴ እና ሌሎች የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የጉምሩክ ኮሚሽን ያከናወናቸውን የለውጥ ስራዎች በዛሬው ዕለት በዋነው /ቤት ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ንግግር ያደረጉት የገቢዎች ሚኒስትር / ዓይናለም ንጉሴ የጉምሩክ ኮሚሽን የሰራቸው ሁለንተናዊ የለውጥ ተግባራት ለሌሎች ሴክተር /ቤቶች ምሳሌ የሚሆኑና ሀገራችን የያዘችውን የብልፅግና ጉዞ እውን ለማድረግ የሚረዱ ናቸው ብለዋል፡፡ ምቹ የስራ አካባቢን ከመፍጠር አኳያም ኮሚሽኑ የሰራቸው የለውጥ ስራዎች አመራርና ሰራተኛው በስራ ቦታው ምቾት እንዲሰማውና የላቀ ውጤት ለማምጣት እንዲነሳሳ የሚያስችሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ሚኒስትሯ አክለውም ኮሚሽኑ የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን ተግባራዊ ያደረጋቸው የወረቀት አልባ አገልግሎቶች ደንበኞች ባሉበት ቦታ ሆነው የሚፈልጉትን አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ እና በአለማቀፍ ደረጃም ተወዳደሪ የሚያደርጉ ስራዎች ናቸው ብለዋል፡፡ በኮሚሽኑ የተደረጉ የለውጥ ስራዎች በገቢዎች ሚኒስቴርም እንዲተገበሩ ሚኒስትሯ አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቃበታ በበኩላቸው በጉምሩክ ኮሚሽን የተከናወኑ ሁለንተናዊ የለውጥ ስራዎች ጠንክረን በጋራ ከሰራን ሀገራችን በምትፈልገው በሁሉም ዘርፍ የላቀ ውጤት ማምጣት እንደሚቻል ማሳያዎች ናቸው ብለዋል፡፡ ኮሚሽኑ ከዚህ የበለጠ ውጤት ለማምጣትም የትኩረት አቅጣጫዎችን ለይቶ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነም ኮሚሽነር ደበሌ  ገልፀዋል፡፡

ኮሚሽነር ደበሌ አክለውም ኮሚሽኑ የያዝነውን 2015 በጀት ዓመትየልህቀት ዓመትብሎ በመሰየም እንደተቋም በሁሉም ዘርፍ ልህቀትን ለማረጋገጥ እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡

Asset Publisher

ዜና

  • የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ Fri, 29 Mar 2024
የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
  • በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል Mon, 18 Mar 2024
በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል
  • የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ Fri, 15 Mar 2024
የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

Asset Publisher

Untitled Basic Web Content

Nested Applications

Asset Publisher

.