Asset Publisher

null የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ

መጋቢት 19/2016 . (የገቢዎች ሚኒስቴር)

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የታክስ ሰርዓቱን ለማዘመን የወረቀት አሰራሮችን የሚያስቀር  የኤሌክትሮኒክስ ኢንቮይስ ሲስተም አስተዳደር  ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችል ሰነድ  ከከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር ጋር ተፈራርሟል::

ስምምነቱን  የገቢዎች ሚኒስትር / አይናለም ንጉሴ እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር / ትግስት ሀሚድ ፈርመዋል::

በስምምነቱ ላይ የገቢዎች ሚኒስትር / አይናለም ንጉሴ  በህገ ወጥ ንግድ በቀረጥ እና ታክስ ማጭበርበር ምክንያት የኢትዮጽያ ኢኮኖሚ መሰብሰብ ያለበትን ገቢ ለመሰብሰብ አለመቻሉን አመላክተው ይህ ስርዓት  የግብይት ደረሰኝን ከአንድ አካል ብቻ ማለትም ከገቢዎች ሚኒስቴር ብቻ እንዲቆረጥ በማድረግ በሃሰተኛ ደረሰኝ የሚደረግ ማጭበርበርን የሚያስቀር ነው ብለዋል::

ሚኒስትሯ  ስርዓቱ ለነጋዴው ማሕበረሰብም ሆነ ለሸማቹ ከፍተኛ ጥቅም የሚሰጥ እንደሆነ ተናግረው የነጋዴው ማህበረሰብ ለደረሰኝ ሕትመት የሚያወጣውን ወጪና ጊዜ ከማስቀረቱም በላይ የግብይት ሂደቱን በቀጥታ ለመከታተልና ለመቆጣጠርም እንደሚያስችል ገልፀዋል፡፡

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት  አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር / ትግስት ሀሚድ በበኩላቸው የሚዘረጋው  የኤሌክትሮኒክስ ኢንቮይስ ሲስተም  ስርዓት የማንዋል የደረሰኝ አስተዳደር ስርአት ወደኤሌክትሮኒክስ የደረሰኝ አስተዳደር ስርአት ለመቀየር የሚያስችል እንዲሁም የዲጂታል ግብይት ስርአቱን በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳልጥ   መሆኑን አንስተው የሚዘረጋው ስርዓት ውጤታማ እንዲሆን የተቻለው ጥረት ሁሉ እንደሚደረግም ተናግረዋል::

Most Viewed Assets

በብዛት የተነበቡ ዜናዎች

  • "ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው Fri, 29 Oct 2021
"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
  • "የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር) Wed, 4 Jan 2023
"የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)