በዘጠኝ ወር ውስጥ ከ212.4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ

213 የበጀት ዓመት ከሐምሌ - መጋቢት 30 ባሉት ዘጠኝ ወራት ውስጥ 213 ቢሊዮን 85 ሚሊዮን 48 262 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ ብር 212 ቢሊዮን 473 ሚሊዮን 364 61 ለመሰብሰብ ተችሏል፡፡ አፈጻጸሙም 99.36 በመቶ ሆኗል፡፡

እቅድ አፈጻጸሙ 212 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የብር 29 ቢሊዮን 225 ሚሊዮን 528 145 ወይም 15.95 በመቶ ዕድገት አለው፡፡

ገቢውም ከሀገር ውስጥ ታክስ ብር 128 ቢሊዮን 171 ሚሊዮን 912 306 ከውጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ ብር 84 ቢሊዮን 135 ሚሊዮን 403 672 እንዲሁም ከሎተሪ ሽያጭ ብር 166ሚሊዮን 48 82 በድምሩ 212 ቢሊዮን 473 ሚሊዮን 364 061 ለመሰብሰብ ተችሏል፡፡

ይህ አፈጻጸም የተመዘገበው ሀገራችን በጸጥታና በኮሮና ወረርሽኝ ውስጥ ባለችበት አስቸጋሪ ወቅት በመሆኑ የተሻለ አፈጻጸም ሊባል የሚችል ነው፡፡

ለዚህ መልካም ውጤት መመዝገብ በወቅቱ ግብራቸውን የከፈሉ ግብር ከፋዮች፤ የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የጉምሩክ ኮሚሽን፣ የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አመራሮችና ሠራተኞች እንዲሁም የሌሎች አጋር አካላት ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይም የጋራ ጥረታችንን ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

.

በብዛት የተነበቡ ዜናዎች

  • "ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው Fri, 29 Oct 2021
"ከፍተኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ህግን በማክበርና የልዕቀት ማዕከል በመሆን አርአያ ሊሆኑ ይገባል" የገቢዎች ሚኒስትር አቶ ላቀ አያሌው
  • "የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር) Wed, 4 Jan 2023
"የሀገራችንን ኢኮኖሚ በጽኑ መሰረት ላይ ለማቆም በሚደረገው ጥረት የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን ያላቸው ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ለአፍታም ቢሆን ሳናሸልብ ተግተን እንሰራለን " ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)