በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከ93 ቢሊየን ብር በላይ ተሰብስቧል

Nested Applications

Asset Publisher

null በመጀመሪያ ሩብ ዓመት ከ93 ቢሊየን ብር በላይ ተሰብስቧል

ከሐምሌ 1/2014 እስከ መስከረም 30/2015 ዓ.ም ወይም ባሳለፍነው ሩብ የበጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ ታክስ እና ከወጪ ንግድና ቀረጥ 93 ቢሊየን 348.46 ሚሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ አስታወቁ፡፡
አፈጻጸሙ ከተያዘው የ95 ቢሊየን 184.36 ሚሊየን ብር ዕቅድ አንጻር የ98.07 በመቶ ክንውን ያስመዘገበ ሲሆን ይህ፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 70 ቢሊየን 39.66 ሚሊየን ገቢ አኳያ በ23 ቢሊየን 308.49 ሚሊየን ብር ወይም በ33.28 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ሚኒስትሯ ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ተናግረዋል፡፡
ሚኒስትሯ አክለውም ከተሰበሰበው ገቢ ውስጥ የሀገር ውስጥ ገቢው ድርሻ 51 ቢሊየን 576.94 ሚሊየን ብር ሲሆን አፈጻጸሙ ከተያዘው የ50 ቢሊየን 21.64 ሚሊየን ብር ዕቅድ አንጻር የ1 ቢሊየን 555.3 ሚሊየን ብር ወይም የ103.5 በመቶ ክንውን አስመዝግቧል፡፡ ይህ፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 38 ቢሊየን 762.45 ሚሊየን ገቢ አኳያ በ12 ቢሊየን 814.49 ብር ወይም በ33.06 በመቶ ዕድገት አሳይቷል ብለዋል፡፡
በወጪ ንግድና ቀረጥ በኩል፤ 41 ቢሊየን 771.52 ሚሊየን ብር ገቢ የተገኘ ሲሆን ከተያዘው የ45 ቢሊየን 162.72 ሚሊየን ብር እቅድ አኳያ የ92.49 በመቶ ክንውን አሳይቷል፡፡ ገቢው ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት 31 ቢሊየን 277.21 ሚሊየን አንጻር በ10 ቢሊየን 494.31 ሚሊየን ብር ወይም በ33.55 በመቶ ዕድገት እንዳለው ሚኒስትሯ አሳውቀዋል፡፡
ሚኒስትሯ ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ የሩብ ዓመቱ አፈጻጸም ሀገራችን በብዙ ፈተና ውስጥ በሆነችበት ጊዜ መመዝገቡ የተሻለ አፈጻጸም ሊያስብለው እንደሚችል እና ግብር ከፋዩንም ሆነ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ሰራተኞች ለተገኘው ውጤት ምስጋና እንደሚገባቸው ጠቁመው በቀሪዎቹ ወራት በ2015 በጀት ዓመት የተያዘውን እቅድ ለማሳካት ብቻም ሳይሆን ካቀድነው በላይ ለመፈጸም ግብር ከፋዮቻችንም ሆነ የግብር ሰብሳቢው ተቋም ሰራተኞች ተቀራርበው በመስራት ለግብር አሰባሰቡ ውጤታማ መሆን ሊረባረቡ እና ሊተጉ ይገባል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Asset Publisher

ዜና

  • የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ Fri, 29 Mar 2024
የገቢዎች ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በዛሬው ዕለት የስምምነት መግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
  • በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል Mon, 18 Mar 2024
በሪፎርም ስራዎች እና በታክስ ሕግ-ተገዥነት ላይ የምክክር መድረክ ተካሂዷል
  • የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ Fri, 15 Mar 2024
የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል የውይይት መድረክ

Asset Publisher

Untitled Basic Web Content

Nested Applications

Asset Publisher

.