ማስታወቂያ
ዜና
በገቢዎች ሚኒስቴር ምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት በግብር ከፋይነት የተመዝግባችሁ እና ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘራችሁ 157 ድርጅቶች በግብር አዋጅ ቁጥር 979/08 እና በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 መሰረት የሚጠበቅባችሁን ግብር/ታክስ የማሳወቅ ግዴታ ባለመወጣታችሁ እንዲሁም ከ23/11/13 – 24/02/14 ዓ.ም ባስመዘገባችሁት አድራሻ የመስክ ክትትል ተደርጎ በንገድ አድራሻችሁ ያለመኖራችሁን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ማንኛውም ግብር ከፋይ ግብር/ታክስ የማሳወቅ ግዴታ ያለበት መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/08 አንቀጽ 10 መሰረት ለውጦች ሲኖሩ የማሳወቅ ግዴታ በሕግ ተጥሏል፡፡ በመሆኑም ቀጥሎ ዝርዝራችሁ የሰፈረ ግብር ከፋዮች ባስመዘገባችሁት አድራሻ ተፈልጋችሁ ያልተገኛችሁ በመሆናችሁ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ30 ቀናት ውስጥ በጽሑፍ ተአማኒነት ያለው ማስረጃ በመያዝ የድሮ ለም ሆቴል አካባቢ የሚገኘው ኮሜት ህንጻ ቁጥር 2 ቀርባችሁ ግብር የማሳወቅ ግዴታችሁን እንድትወጡ እየገለጽን ግዴታችሁን ካልተወጣችሁ ግን በታክስ አስተዳደር አዋጁ ላይ በተቀመጠው የህግ ድንጋጌ መሰረት የወንጀል ተጠያቂነትና ምዝገባን የመሰረዝ ተፈጻሚነትን የሚያስከትል መሆኑን እንሳስባለን፡፡
ለበለጠ መረጃ የፌስቡክ እንዲሁም በቴሌግራም ገጻችን Ministry of Revenues of Ethiopia /የገቢዎች ሚኒስቴር / ይጎብኙ
በገቢዎች ሚኒስቴር ምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት